“….ራዕይ ራዕይ…” ስንል አንዱም ሳይያዝ፣ በመሃከል ያንድ ሰው እድሜ አለፈ። ኢትየጵያም አሁን ጥናቶች እነደሚመሰክሩት ” ከድንቁርናና ከድህነት ፈጽሞ አልተላቀቀችም።” በጣት የሚቆጠሩ ጥቂት ሰዎች በሀገራችን በኢትዮጵያ ከልክ በላይ ስላለፈላቸውና ጠግበው ስላደሩ፣ ህዝቡ ጠግቦ ያደረና የተመቸው የሚመስላቸው አሉ።
ዛሬ ሁሉንም ዜጋና ወገን እንደ ማንኛውም የዓለም ሕዝብ በአገሩ የፖለቲካና የኢኮኖሚ መድረክ ሚያሳተፍበት ግልጽ የሆነ የነጻነትና የልማት የዕድገት ፕሮግራም የለም። የግል ሐብት፣የመሬት ባለቤትንት መብት ክልክል ነው። ሕገ መንግሥቱ ላይ የሰፈሩት ሰበአዊ መብቶች በሥራ በትክክል አልተተረጎሙም።
የፕሬስ ነጻነት የለም። የግለ ሰቦች መብቶች -አንድ ሰው የፈለገውን ለመከተል፣ለመተቸት፣ለመቃወምና ለመደገፍ፣ለመሰብሰብና ለመደራጀት-ይህ ሕገ-መንግሥቱ ላይ የሰፈረው መብቱ አይከበርም ። የነጻ-ፍርድ ቤትና የነጻ-ዳኛ ጉዳይ አለ።አንድ ሰው ጠበቃ ይዞ በሥነ-ሥርዓቱ ሳይከራከርና በጥፋቱ ሳይፈረድበት ይወነጀላል።…
ግን ምንነቱ የማይታወቅ፣ ብዙዎቹ እንደሚሉት፣እሰከ አሁን ድረስ ምንም በቂ ማብራሪያ ያልተሰጠው „ …ራዕይ አለ እሱን ተከተሉ” እንባላለን።
ይህ ” የአቶ መለሰ ራዕይ…የተባለው ሰነድ ” አንድም ቦታ ተጠርዞ ሲበተን አላየንም። ምን ዓይንት መልዕክቶችን እንደያዘም እኛ በዝርዝር የምናውቀው ነገር የለም።
ይህን ጉዳይ አስመልክቶ “ዶቸ ቬለ-የጀርመን ራዲዮ ጣቢያ ” ስለ ጊዜያዊው የኢትዮጵያ ሁኔታ አዘጋጅቶት የነበረውን አጠር ያለ ውይይት፣ እንድታደምጡት፤ መጽሔቱ „ለአእምሮ “ ይጋብዛችሁዋል።
—————————————————-
አስተያየት ለመስጠት / Comments
——————————–
——————–
© ለ አእምሮ 2005 / © Le’Aimero Copyright 2013